ፈረስ ለጭነት መጠቀም 60 ሺህ ብር ያስቀጣል‼️

ፈረስ ለጭነት መጠቀም 60 ሺህ ብር ያስቀጣል‼️


                                                                            
የፊቼ ከተማ አስተዳደር

የፊቼ ከተማ አስተዳደር ፈረስን ለጭነት አገልግሎት ማዋል በገንዘብ የሚያስቀጣ ተግባር ይሆናል ብሏል።

የከተማ አስተዳደሩ ከአራት ወራት በኋላ ተፈጻሚ የሚሆነውን መመሪያ በመጣስ ፈረስን ለጋሪ አገልግሎት ተጠቅሞ የተገኘ በ60 ሺህ ብር ይቀጣል ብሏል።

የከተማ አስተዳደሩ ከዚህ ውሳኔ የደረሰው ፈረስ በኦሮሞ ባሕል ያለውን ክብር እና ቦታ ዝቅ በማድረግ ለስቃይ እየተዳረገ በመሆኑ ነው ይላል።

በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን የምትገኘው የፊቼ ከተማ የባሕል ና ቱሪዝም ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አበራ ደጀኔ “ፈረስ፤ ጋሪ መጎተት የለበትም። ፈረስ ክብር አለው፣ በኦሮሞ ባሕል ትልቅ ቦታ አለው። በማይገባው ቦታ መገኘት የለበትም” ሲሉ ለቢቢሲ ተናግረዋል።

አስተያየት ይለጥፉ

አዲስ የድሮ

Blog ads

Betseb media