የኢትዮጵያ አየር መንገድ

                                                                 የኢትዮጵያ አየር መንገድ

 

 
በአፍሪካ ግንባር ቀደም የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ በ2016 በጀት አመት የመጀመሪያ እሩብ ያስመዘገበው ትርፍ ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት በ 55 በመቶ እድገት አሳየ‼️
ከሀምሌ እስከ መስከረም ባሉት ሶስት ወራት አየር መንገዱ ከ 19.5 ቢሊየን ብር በላይ ትርፍ ከታክስ በፊት ያስመዘገበ ሲሆን ይሄም ከእቅዱ በላይ 18 በመቶ ጭማሪ እንዲሁም ከቀዳሚው አመት ተመሳሳይ ወቅት የ 55 በመቶ ጭማሪ የታየበት ነው፡፡

በተመሳሳይ በተጠቀሰው ጊዜ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ገቢው 102 ቢሊየን ብር ነበር፡፡ ይህም ከ2015 ተመሳሳይ ሩብ አመት የ21 በመቶ ጭማሪ የተመዘገበበት ነው፡፡

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ይፋ ባደረገው መረጃ አየር መንገዱ በሩብ አመቱ ወደ 4.5 ሚሊየን የሚሆኑ መንገደኞችን ያጓጓዘ ሲሆን ይህም ከእቅዱ 102 በመቶ እንዲሁም ከቀዳሚው አመት 36 በመቶ ጭማሪ የታየበት ነው፡፡

አስተያየት ይለጥፉ

አዲስ የድሮ

Blog ads

Betseb media